ሁሌ ተደናግጦ
- ሁሌ ተሸብሮ፣
በፀየፈ ተግባር
- ሁሌ አቀርቅሮ፣
ሲወጡ ሰገቡ
- ሁሌ ተደብቆ፣
ፍቅር ካላገኙ
- ከሰው ጋር
ተኑሮ፣
ስህተት ካላረሙ
- ካለፉት ተምሮ፣
ሰው መባል ምንድነው?
.... የቱስ ላይ
ነው ኑሮ!?
ሰው እውነትን
ንቆ!?
.በሐሰት ተዘፍቆ፣
ከእሱነት መለያው
ከሕሊናው ርቆ፣
ከጊዚያዊ ስጋው
- ከንዋይ ተጣብቆ፣
ከነገ ክቡር
ስም - የዛሬ
ሆድ ልቆ፣
ደስታን ሳያሸቱ
- ከሕዝብ ጋር
ስቆ፣
ገላን ለይስሙላ
- በከፈን ደብቆ፣
ሁልጊዜ ተጨንቆ
- ሁልጊዜ ተሰቆ፣
እንኳን በሐገር
ላይ - ባህር
ማዶ ርቆ፣
አዳራሽ ለመግባት
- ዙርያ ተጠብቆ፣
ሲገቡ በጓሮ
- ሲወጡ በጓሮ፣
ኑሮ ነው አትበሉኝ
- የቱ ላይ ነው
ኑሮ!!
የቋጠሯትስ
ብር - መቼ ቀን
ተበልቶ፣
ምን ቀን ተረጋግቶ
- ሁሌ እንቅልፍን
አጥቶ፣
ታዲያ
ስው ራሱን አስሮ
- ነፃነቱን
አጥቶ፣
ሰውን እንዴት
ያስራል - ምን
አቅም አግኝቶ!?
ሽቦ
አጥር ቢያጥሩ
- ብረት ቢከምሩ፣
ፈራሽ ገላን
እንጂ - እውነትን
አያስሩ፣
ቢሮ ቢሰብሩ
እንጂ - መንፈስን
አይሰብሩ፣
ጉዞ የጀመረን
የነፃነት እሳት
...
... ለአፍታ ቢገቱ
እንጂ - ጨርሰው
አይቀብሩ፣
እናም አስተማሩ፣
በሕዝብ ደም
ሰርፀው - እነዚህ
ሲኮሩ፣
ዓለም ሳቀባቸው
- እነዚያ አፈሩ፣
.. እና መች ታሰሩ!?
እስቲ እንለየው
- ማን ነው የታሰረው!?
እነዚያ ተበተን
ተለያዩ ሲሉ፣
እነዚህ በፍቅር
አንድ እንሁን
አሉ፣
እነዚያ ጥላቻን
ቂም ሲያቆጣጥሩ፣
እንዚህ ምህረትን
...
ይቅር መባባልን
- ፍቅርን አስተማሩ፣
እነኚያ በሃይል
- በጥይት ሲያመልኩ፣
እነዚህ በብዕር
- ጥይት ይቅር
አሉ፣
ሃገርህን ጥለህ
- ተሰደድ ሲባሉ፣
ለጊዚያዊ ጥቅም
- ለሆድ ሳያደሉ፣
ደስታውም ሐዘኑም
..
ከሕዝባችን
ጋራ ባገራችን
አሉ፣
እነኚያ ተጨንቀው
- እንዲያው ሲያስመስሉ፣
ከሚድያ ጀርባ
- አለን አለን
ሲሉ፣
ያብሮነትን
ክብር - እነዚህ
አሳዩ፣
ሆ .! እያለላቸው
- ምድር ሳር ቅጠሉ፣
ሕዝብ መሃል
ገብተው ፍቅር
ይህ ነው አሉ፣
እናም ሰርፀው
ገቡ፣
በሕፃን በአዛውንቱ
እየተሞገሱ፣
ስያሜ እስኪቸግር
- መንፈስ እስኪባሉ፣
በጠለቀ ቅርበት
- አካሌ ተባሉ፣
እናም በሕዝባችን
በደሙ ውስጥ
አሉ፣
ታድያ መች ታሰሩ?
- ማን ነው የታሰረው?!
እነዚያ ተጨንቀው
- እንዲህ ሲዳክሩ፣
ለሃሰት ውንጀላ
- አለት ሲቆፍሩ፣
ምስክር በሆዱ
- በእራፊ ሲቀጥሩ፣
በበጎ ሥራቸው
- እነዚህ ግን
ኮሩ፣
ካገራቸው አልፈው
- ለዓለም በዋሉ፣
በዚህ ሰአት
እንኳ - ሃገርን
አስጠሩ፣
እነዚያ እንዳሉት
- ሃገርም አልካዱ
.... ዘርም አላጠፉ፣
ይልቅ ዘር ያጠፋን
- ሊዳኙ ሄዱ እንጂ
.. እውነትን ሊያጣሩ
ዓለም ይህን
ሲያውቀው ፣
በገሃድ እያየው፣
እየመሰከረ
እየሸለማቸው!
አሰርን ይላሉ
- ጉድ እማይከብዳቸው!
... በርግጥ ቢጨንቃቸው
፣
መላ ቢጠፋ እንጂ
- አይገፉት ገጥሟቸው፣
የሚሰሩት ስራ
- ሀቁ መች ጠፋቸው፣
ተከሳሽ ተገርሞ
- እየሳቀባቸው
፣
ጠበቃም አናቆም
- ብሎ ሲንቃቸው፣
ችሎት ተደናግጦ
- ተጨነቀባቸው::
እናስ ወገኖቼ
- ማን ነው የታሰረው?!
መታሰር ምንድነው?!
በብረት መካለል
- የዓመታት ፍዳው፣
አለመለመ እንጂ
- ይበልጥ አጎመራው፣
የማንዴላን
ትግል - ማን ጀግና
ቀበረው!?
እና እስኪነቁ
እንጂ .
.. ሰው መሆን
ገብቷቸው፣
እነኚህ ሥራ
ላይ ተልዕኮ
ላይ ናቸው፣
ቀልጦ እሳት
መሆንን - ሞቶ
ሰው ማዳንን
፣
ታስሮ ማስፈታትን
እያስተማሯቸው
ጀግኖቹስ ሥራ
ላይ ተልዕኮ
ላይ ናቸው፣